cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

TIKVAH-ETHIOPIA

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው። @tikvahuniversity @tikvahethAfaanOromoo @tikvahethmagazine @tikvahethsport @tikvahethiopiatigrigna #ኢትዮጵያ

Show more
Advertising posts
1 354 401
Subscribers
+11524 hours
+3 2957 days
+16 24430 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

Photo unavailableShow in Telegram
በኢራን የሂሊኮፕተር አደጋ የሞቱት እነማን ናችው ? - የኢራን ፕሬዝዳንት ኢብራሂም ራይሲ - የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆሴን አሚር አብዶላሂያን - የተብሪዝ መስጂድ ኢማም አያቶላህ አልሃሸሚ - የምስራቅ አዘርባጃን ግዛት አስተዳዳሪ ማሊክ ራህማቲ - የፕሬዝዳንቱ ጥበቃ ኃላፊ ማሄዲ ሙሳቪ - የሄሊኮፕተሩ አብራሪ፣ - የሂሌኮፕተሩ ረዳት አብራሪ - ቦዲጋርድ - የበረራ አስተናጋጅ በትላንቱ የሂሊኮፕተር አደጋ ሞተዋል። የፕሬዜዳንት ራይሲን ሞት ተከትሎ ምክትል ፕሬዜዳንቱ ሞሀመድ ሞክበር በ50 ቀናት ውስጥ በምርጫ አዲስ ፕሬዜዳንት እስኪመረጥ ድረስ የፕሬዜዳንቱን ቦታ ተክተው ይሰራሉ። @tikvahethiopia
Show all...
😢 1116😭 511👏 111 81🙏 49🕊 42😱 38🤔 19😡 19🥰 14
#ኢራን የኢራን ፕሬዚዳንት ኢብራሂም ራይሲ ተሳፍረውባት በነበረው ሄሊኮፕተር በደረሰው አደጋ ህይወታቸው አልፏል። ይህንንም የሀገሪቱ የመንግሥት ሚዲያ አረጋግጧል። ከሳቸው በተጨማሪ በሂሊኮፕተር ውስጥ አብረው የነበሩት የአገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆሴይን አሚር አብዶላሂያን እና ሌሎች በርካታ ሰዎች ሞተዋል። ሮይተርስ በአደጋው ፕሬዚዳንቱ ሲጓዙባት የነበረችው ሄሊኮፕተር _ ሙሉ በሙሉ መቃጠሏን " አንድ የኢራን ባለስልጣንን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል። " የፕ/ት ራይሲ ሄሊኮፕተር በአደጋው #ሙሉ_በሙሉ ተቃጥላለች። በሚያሳዝን ሁኔታ ሁሉም ተሳፋሪዎች ሳይሞቱ አልቀሩም " ብለዋል ስማቸው ያልተጠቀሰው ባለስልጣን። #BBC @tikvahethiopia
Show all...
😭 1132👏 115🕊 48 38😱 38😢 36🥰 12😡 12🙏 6
Photo unavailableShow in Telegram
#Tecno #Camon30Pro5G ቪድዮዎች እና ምስሎችን በከፍተኛ ጥራት ማንሳት እንዲያስችል Sony Imx890 የካሜራ ሴንሰርን የተገጠመለት አዲሱ Tecno Camon Pro 5G ምርጫዎ ያድርጉ #Camon30Et #Camon30pro5GEt #Camon30 #Camon30Pro5G #TecnoEt
Show all...
26😱 7
Photo unavailableShow in Telegram
ሕብር የሴቶች የቁጠባ ሒሳብ - ለአንቺ የሚገባሽ! ሕብር የሴቶች የቁጠባ ሒሳብ ከመደበኛው የቁጠባ ሒሳብ ላቅ ያለ ወለድ የምታገኚበት! ሕብረት ባንክ በሕብረት እንደግ! ለበለጠ መረጃ ወደ 995 ነፃ የጥሪ ማዕከል ይደውሉ፡፡ አዳዲስ መረጃ እንዲርሶ የሚከተሉትን ማስፈንጠሪያዎች ይጫኑ፡፡ ቴሌግራም- https://t.me/HibretBanket ሊንክዲን- https://www.linkedin.com/company/hibretbank/ ዌብሳይት- https://www.hibretbank.com.et/ #Hibretbank
Show all...
14🕊 1
#IRAN🇮🇷 የኢራኑ ፕሬዝዳንት እና አብረዋቸው የነበሩ ከፍተኛ ባለስልጣናት (የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩን ጨምሮ) እየተፈለጉ ነው። ህዝቡ መሪዎቹ ምንም ሳይሆኑ በህይወት ተርፈው ይመለሱ ዘንድ ፈጣሪውን እየለመነ ይገኛል። ፕ/ት ኢብራሂም ራኢሲ እና ሌሎች ባለስልጣናት ኢራን ከአዘርባጀን ጋር በምትዋሰንበት አካባቢ ላይ የተገነቡ 2 ግድቦችን መርቀው ከከፈቱ በኋላ በሂሊኮፕተር ወደ ታብሪዝ ከተማ ሲያመሩ ነው ደብዛቸው የጠፋው። ሄሊኮፕተሯ በአስቸጋሪ የአየር ሁኔታ ሳቢያ ከተራራ ጋር እንደተጋጨች ተነግሯል። ሂሊኮፕተሯ ተጋጭታለች የተባለበት #ትክክለኛው ቦታ እስካሁን ድረስ ባይለይም ተጋጭታለች ተብሎ በታሰበበት እያንዳንዱ ቦታ ላይ ግን የነፍስ አድን ርብርብ እየተደረገ ይገኛል። የአየር ሁኔታው ግን እጅግ በጣም ከባድ እንደሆነ ተሰምቷል። ቪድዮ፦ ቀን እና ማታ ላይ የነበረውን የህዝቡን ሁኔታ የያሳያል። @tikvahethiopia
Show all...
😭 1108🙏 205 149👏 99🕊 65😱 37😢 34🥰 31😡 31🤔 26
#ስፖርት ማንችስተር ሲቲ የእንግሊዝ ፕሪሜየር ሊግ 2023/2024 ሻምፒዩን ሆነ። ቡድኑ በተከታታይ ለ4 ዓመታት የፕሪሚየር ሊጉን ዋንጫ በማንሳት አዲስ ታሪክ ጽፏል። ዘንድሮ እስከ ዛሬው የመጨረሻ መርሀግብር ከ #አርሴናል ጋር አንገት ለአንገት የተናነቀው ሲቲ 91 ነጥብ በመሰብሰብ ነው ዋንጫውን ያሸነፈው። እጅግ ብርቱ እና ጠንካራ አመትን ያሳለፈው አርሴናል 89 ነጥብ በመያዝ በሁለተኛነት ማጠናቀቅ ችሏል። አርሴናል ባለፈው አመትም ለዋንጫ ተቃርቦ ዋንጫውን ማግኘት ሳይችል መቅረቱ አይዘነጋም። ዘንድሮም በ2 ነጥብ ተበልጦ ዋንጫውን ሳያገኝ ቀርቷል። ሊቨርፑል አመቱን በ3ኛነት ሲያጠናቅቅ አስቶን ቪላ 4 ፣ ቶተንሃም 5 እንዲሁም ቼልሲ 6 ሆነው ጨርሰዋል። ባለ ብዙ ታሪኩ ማንቸስተር ዩናይትድ እጅግ በጣም ደካማ የተባለ አመትን በማሳለፍ በታሪኩ ዝቅተኛ የተባለው 8ኛ ደረጃ ይዞ ጨርሷል። የእንግሊዝ ፕሪሜየር ሊግ በመላው ዓለም በብዙ ሚሊዮን ተመልካችን ማግኘት የቻለ ጠንካራ የእግር ኳስ ፍልሚያ ሲሆን በሀገራችን #በኢትዮጵያም ሚሊዮኖች በተለይ ወጣቶች ውድድሩን ይከታተሉታል። ቲክቫህ ስፖርት https://t.me/+VvwzStMNcNHmhK0x @tikvahethiopia
Show all...
1532😭 574👏 212😡 146🙏 65🥰 49😢 49🕊 28🤔 23😱 12
00:28
Video unavailableShow in Telegram
#ኢራን የኢራን ፕሬዝዳንት የሆኑት ኢብራሂም ራኢሲ ሲጓዙበት የነበረ ሄሊኮፕተር " #በአደገኛ_ሁኔታ " መሬት ላይ ማራፉን የኢራን መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። የሀገሪቱ ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ሂሊኮፕተሩ በአደገኛ ሁኔታ አርፎበታል ወደተባለበት ስፍራ ላይ አስቸጋሪ የአየር ሁኔታ እንዳለ ገልጿል። የነፍስ አድን ሠራተኞች ወደ ቦታው ለመድረስ ጥረት እያደረጉ ይገኛሉ ሲል አሳውቋል። ፕሬዝዳንቱ ሀገራቸው ከአዘርባጀን ጋር በምትዋሰንበት አካባቢ የተገነቡ ሁለት ግድቦችን መርቀው ከከፈቱ በኋላ ወደ ሰሜን ምዕራቧ የአገሪቱ ከተማ ታብሪዝ እያመሩ ነበር። ሄሊኮፕተሩ አርፎበታል በተባለው ስፍራ ላይ ባለው ከባድ ጭጋግ ምክንያት የነፍስ ማዳን ፍለጋ ሥራው አስቸጋሪ እንደሆነ ተነግሯል። Credit - FARS @tikvahethiopia
Show all...
😢 524😱 116 92👏 47😭 46🙏 36🕊 33🤔 28🥰 22
የታገተችው ታዳጊ ጉዳይ ከምን ደረሰ ? ታግታ ከተወሰደች በኃላ ለማስለቀቂያ 3 ሚሊዮን ብር የተጠየቀባት የታዳጊዋ ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ጉዳይ እስከአሁን እንቆቅልሽ ሆኖ ቀጥሏል። መጋቢት 10 ቀን 2016 ዓ.ም በዓድዋ ከተማ ልዩ ቦታው " ዓዲ ማሕለኻ " ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ታግታ የተሰወረችው ታዳጊ ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ከታገተች ዛሬ ግንቦት 10/2016 ዓ.ም 60 ቀናት አስቆጥራለች። ታጋች ታዳጊዋ እስከ አሁንዋ ደቂቃ ሰአትና ቀን አልመገኘትዋን ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል እገታ ወደ ተካሄደበት ከተማ ድረስ በመሄድ አረጋግጧል። የመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባል ፥ ዓድዋ ድረስ በመጓዝ ወላጅ አባትዋን እና ቤተ ዘመድ ጠይቆ ባገኘው መረጃ የታዳጊዋ የእገታ ጉዳይ ከትግራይ የፀጥታ አካላት አልፎ የፌደራል የፀጥታ አካላትም እንዲያውቁት ተደርጓል። የዓድዋ ከተማ ፓሊስ ከሳምንታት በፊት ታጋችዋን ታዳጊ ለማስለቀቅ ከከተማ እስከ ክልል የተቀናጀ የክትትልና ምርመራ ስራ እየሰራን መሆኑና በቁጥጥር ስር የዋሉ ተጠርጣሪዎች እንዳሉ ገልጾ ነበር። የታዳጊዋን መታገት በማስመልከት ቤተሰቦችዋ መጋቢት 10 ቀን 2016 ዓ.ም ሪፓርት ካደረጉበት ቀንና ሰዓት ጀምሮ ፓሊስ ጉዳዩን ለደቂቃ ያህል ችላ እንዳላለው ገልጾ የነበረ ቢሆንም አሁንም ድረስ ጉዳዩ መቋጫ ሳያገኝ ይሄው 60 (ሁለት ወር) ተቆጥረዋል ሲሉ የማህሌት ወላጅ አባት ተኽላይ ግርማይ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል። " የህግ አካላት የክትትል እና ምርመራ መላላት የልጃችን አጋቾች በህግ ቁጥጥር ስር እንዳይውሉ ምክንያት ሆኗል " ያሉት ወላጅ አባት አቶ ተኽላይ " በአንዲት ትንሽ ከተማ የተፈፀመ የእገታ ወንጀል በምንም መመዘኛ ከክልሉና የፌደራል የፀጥታ አካላት አቅም በላይ ሊሆን አይችልም " ሲሉ አክለዋል። #TikvahEthiopiaFamilyMekelle @tikvahethiopia
Show all...
😭 834 107😢 90🕊 46🙏 39🥰 21😱 20😡 18🤔 17👏 15
የታገተችው ታዳጊ ጉዳይ ከምን ደረሰ ? ታግታ ከተወሰደች በኃላ ለማስለቀቂያ 3 ሚሊዮን ብር የተጠየቀባት የታዳጊዋ ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ጉዳይ እስከአሁን እንቆቅልሽ ሆኖ ቀጥሏል። መጋቢት 10 ቀን 2016 ዓ.ም በዓድዋ ከተማ ልዩ ቦታው " ዓዲ ማሕለኻ " ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ታግታ የተሰወረችው ታዳጊ ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ከታገተች ዛሬ ግንቦት 10/2016 ዓ.ም 60 ቀናት አስቆጥራለች። ታጋች ታዳጊዋ እስከ አሁንዋ ደቂቃ ሰአትና ቀን አልመገኘትዋን ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል እገታ ወደ ተካሄደበት ከተማ ድረስ በመሄድ አረጋግጧል። የመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባል ፥ ዓድዋ ድረስ በመጓዝ ወላጅ አባትዋን እና ቤተ ዘመድ ጠይቆ ባገኘው መረጃ የታዳጊዋ የእገታ ጉዳይ ከትግራይ የፀጥታ አካላት አልፎ የፌደራል የፀጥታ አካላትም እንዲያውቁት ተደርጓል። የዓድዋ ከተማ ፓሊስ ከሳምንታት በፊት ታጋችዋን ታዳጊ ለማስለቀቅ ከከተማ እስከ ክልል የተቀናጀ የክትትልና ምርመራ ስራ እየሰራን መሆኑና በቁጥጥር ስር የዋሉ ተጠርጣሪዎች እንዳሉ ገልጾ ነበር። የታዳጊዋን መታገት በማስመልከት ቤተሰቦችዋ መጋቢት 10 ቀን 2016 ዓ.ም ሪፓርት ካደረጉበት ቀንና ሰዓት ጀምሮ ፓሊስ ጉዳዩን ለደቂቃ ያህል ችላ እንዳላለው ገልጾ የነበረ ቢሆንም አሁንም ድረስ ጉዳዩ መቋጫ ሳያገኝ ይሄው 60 (ሁለት ወር) ተቆጥረዋል ሲሉ የማህሌት ወላጅ አባት ተኽላይ ግርማይ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል። " የህግ አካላት የክትትል እና ምርመራ መላላት የልጃችን አጋቾች በህግ ቁጥጥር ስር እንዳይውሉ ምክንያት ሆኗል " ያሉት ወላጅ አባት አቶ ተኽላይ " በአንዲት ትንሽ ከተማ የተፈፀመ የእገታ ወንጀል በምንም መመዘኛ ከክልሉና የፌደራል የፀጥታ አካላት አቅም በላይ ሊሆን አይችልም " ሲሉ አክለዋል። #TikvahEthiopiaFamilyMekelle @tikvahethiopia              
Show all...
#AddisAbaba ገንዘብ ለማግኘት ሲሉ ብቻ ምንም ሳይታመሙ " ታመናል " ወይም ልጃቸው / ቤተሰባቸው ሳይታመም እንደታመመ አስመስለው እርዳታ የሚጠይቁ ሰዎች በትክክል ሊረዱ የሚገባቸው ሰዎችን እንዳይረዱ ያደርጋሉ። ከዚህ ቀደም በውሸት ገንዘብ በእርዳታ መልክ ሲሰበስቡ ስለተያዙ ሰዎች መረጃ መለዋወጣችን አይዘነጋም። ትላንት ደግሞ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጤናማ ልጁን " የካንሰር ህመምተኛ ነው " በማለት ሲለምንበት የተገኘ ወላጅን እና ግብረ-አበሩን ይዞ ምርመራ እያጣራ መሆኑን አሳውቋል። በወንጀሉ የተጠረጠረው አባት (ጃዋር አብዱላሂ) ልጁን የካንስር ህመምተኛ በመሆኑ ለማሳከም ከአዋሽ 7 ወደ አዲስ አበባ መምጣቱንና ልጁን ለማሳከም እና ለምግብ እንዲሁም ለማደሪያ መቸገሩን በመግለፅ ከግብረ-አበሩ (አህመድ ከሊፈ) ጋር በመሆን በአ/አ በተለያዩ ቦታዎች ሲለምን ቆይቷል። ትላንት ግን አንድ የፖሊስ አባል ነገሩን ተጠራጥሮ የህክምና ማስረጃ ሲጠይቃቸው ማሳየት አልቻሉም። ፖሊስም ይዞ ፖሊስ ጣቢያ አስገብቷቸዋል። የህፃኑ አባት እና ግብረ አበሩ ልጁ ታማሚ እንዲመስል አንገቱ ላይ ፕላስተር ለጥፈውበት የነበረ ሲሆን ፕላስተሩ ሲነሳ አንገቱ ላይ ምንም ቁስል የለም። ህፃኑ በፖሊስ ጣቢያ  ሲጠየቅ ጤነኛ መሆኑን ገልጿል። #ኢትዮጵያዊ የተቸገረን ሰው መርዳት የቆየ ባህሉ ነው፤ ካለው ሰው ሲለምነው ጥሎ መሄድን አያውቅም ፤ ነገር ግን በውሸት / በማጭበርበር የሚካሄድ ተግባር እውነተኛ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ሰዎች እንዳይረዱ ያደርጋል። እርዳታ ሲሰጥ የህክምና ማስረጃዎች መጠየቅ ይገባል። @tikvahethiopia
Show all...
😢 328 95😡 68👏 35🥰 10🤔 10🕊 9😭 8😱 7🙏 7